ስደተኞችን ስፓንሰር ለማድረግ የወጣ የምዝገባ ጥሪ

የኢትዮጲያዊያን ማህበር በቶሮንቶና አከባቢው ከካናዳ የዜግነት እና የስደተኞች ጉዳይ መስሪያ ቤት ጋር ሰደተኞችን
ስፓንሰር ለማድረግ ባለው ስምምነት መሰረት በ 2018 ስደተኞችን ስፓንሰር የማድረግ እቅድ አለው።
1. ማህበሩ ስፓንሰር ለማድረግ ያለው ቦታ 7

2. ከስፓንሰር አድራጊው የሚጠበቅ
ከማህበሩ ጋር በሚደረገው ስምምነት መሰረት ስፓንሰር አድራጊ የሚጠበቅበት/ባት ሃላፊነት የሚከተሉት ናቸው
 ለመመዝገቢያ $250 መክፈል (ይህ ክፍያ የማይመለስ ነው)
 ስፖንሰር የሚደረገውን /የምትደረገውን ግለሰብ ውይም የቤተሰብ አባላት መሰረታዊ ወጪን ከመጡበት
ቀን ጀምሮ ለ 12 ወራት ለመሸፈን ፈቃደኛ በመሆን ከማህበሩ ጋር ስምምነት የሚፈርም/የምትፈርም ና
ለዚህም ዋስትና ገንዘብ በቅድሚያ የሚያሲዝ/ የምታሲዝ።
 ስፖንሰር ስድራጊ መሙላት ያለበትን/ያለባትን ቅፆች መሙላት። ለዝርዝሩ
https://www.canada.ca/en/immigration-refugeescitizenship/corporate/publications-manuals/guide-private-sponsorship-refugeesprogram.html ድህረ ገፅ ይመልከቱ።
3. በስደተኞች በኩል መሞላት ያለበት ቅፅ፥
 በስደተኛነት ወደ ካናዳ ስፖንሰር በመሆን ለቇሚ ነዋሪነት Permanent Residence የሚሞሉትን እና
IMM6000 በመባል በሚታወቀው መመሪያ ስር የሚጠቃለሉትን አስፈላጊ ቅጾችን በመሙላት እና
በስፓንሰር አድራጊያችው በኩል ለማህበሩ ማቅረብ።
 ለዝርዝሩ https://www.canada.ca/en/immigration-refugeescitizenship/services/application/application-forms-guides.html ድህረ ገፅ ይመልከቱ።
4. የመመዝገቢያ ቦታ እና ጊዜ
 ቦታ ፡ የኢትዮጵያዊያን ማህበር በቶሮንቶና አከባቢው ጽ/ቤት
1950 Danforth Avenue, East York, ON M4C 1J4
 ጊዜ ፡ May 30, 2018 – June 30, 2018 ከሰኞ እስከ አርብ ከ 12pm እስከ- 5pm